ፖሊስና የደህንነት አባላት የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ አካባቢ የሚገኘውን ህዝብ በር እያንኳኩ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲን በድምጽ ብክለት ክሰሱት!›› እያሉ እየቀሰቀሱ ነው፡፡ ነገር ግን አብዛኛዎቹ የሰፈሩ ነዋሪዎች ‹‹እስካሁን አልረበሹንም፣ ሊረብሹንም አይችሉም፡፡›› እያሏቸው ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እያለ አመራሮቹ ጃን ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ ‹‹ህዝቡ ነው የድምጽ ብክለት አድርሰውብናል በሚል›› የከሰሳችሁ ማለቱ ይታወሳል፡፡
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ በደረሰን መረጃ መሠረት ለእሁዱ የተቃውሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች የመኪናው ቅስቀሳ ጀምሯል፡፡ የመጀመሪያው ቡድን ለቅስቀሳ ወጥቷል፡፡