ጓዶች በአፅቢ ከተማ አራት የዓረና አመራር አባላት ከያዙት አልጋ እንዲለቁ ተጠይቀው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ታስረው አደሩ

April 16, 2014

ጓዶች በአፅቢ ከተማ አራት የዓረና አመራር አባላት ከያዙት አልጋ እንዲለቁለት ጠይቆ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ፖሊስ ጠርቶ ያሳሰራቸው የፌደራል መንግስት ባለስልጣን አቶ ተፈራ ደርበው (የግብርና ሚኒስተር) ነው። የፌደራል ባለስልጣን ሊይዘው የሚገባ አልጋ ይዛችኋል ተብለው ነበር ታስረው ያደሩ። ከአፅቢ የዓረና ስብሰባ በኋላ በአባይ ፀሓየና ስብሃት ነጋ የሚመራ የፌደራል መንግስት ልኡኳን የአፅቢን ህዝብ ችግር ለመፍታት (ወይ ለማባባስ) ተልከዋል። መሬት የህዝብ ይሆናል፣ ብድር በነፃ ነው ወዘተ እያሉ ዓረና ሲያስተምረው የነበረውን ሲሰብኩ ሰንብተዋል። ዛሬ ሰኞ መጋቢት 06, 2006 ዓም ደግሞ አስራአለቃ ስንታየሁ ይመር የተባሉ የዓረና አባል “ዓረና” የሚል ፅሑፍ ያለው ቲ-ሽርት በመልበሳቸው ምክንያት በፖሊስ ታስረው ከሰዓታት በኋላ ተለቀዋል

 

Previous Story

ሰማያዊ በፌደራል መንግስቱና በቡለን ወረዳ የመሰረተው ክስ ሀሙስ ፍርድ ቤት ይቀርባል!

Next Story

የአንበጣ መንጋ በሶማሌ፣ በኦሮሚያና በድሬደዋ ባሉ 13 ወረዳዎች ስጋት ሆኗል

Go toTop