ተስፋ (ከዘላለም ገብሬ)

August 3, 2011

በሃሳብ ተኝተሽ
ሃሳቡን ጸንሰሽ
ጽንሱን አሳድገሽ

የሃሳብ ልጅ አርገሽ

እርግዝናው ሞቆሽ እናትነት ሰቶሽ

የእናትነት ፍቅርን ሃሳብ አስረክቦሽ

ጭንቅ ብሎሽ እርግዝናው ከብዶሽ

መራመድ አቅቶሽ

መውለጃሽ ሲቃረብ

ምጡ ሲጠናበሽ ጩኽትሽ በርትቶ

መውለድም ሲከብድሽ

ተወለድ! አልወለድም ክርክሩ ገጥሞሽ

የእናትነት ጥማት ልጅሽን ተጠምተሽ

የተስፋ ልጅ ይዘሽ ከቶ ማያገኙት

ወልደው የማያዩት ምጡንም አመጠው

በሃሳብ ተክዘው በጭንቀት ተጠበው

የተስፋ ልጅ ይዘው

ነገን ተስፋ አድርገው

በተስፋ ላይ ታዝለው

ተ…….ስ……ፋ…. እያሉ ሲያቆለጳጵሡት ሲያሞጋግሱት

እውነት ህይወት መስለሽ እንዲህ ያደረገሽ

የነገን ሰንቆ ዛሬ ህልም አስይቶሽ

ባዶነት መኖሩን ምኑንም ሳይነግርሽ

ልብሽን ወጥሮ አእምሮሽን ሰብሮ

በደስታ ፍሬ የዘርፍሬ አጭደሽ

በተስፋ ማእበል የህልም ጉዞ ሄደሽ

መቼም ላትመለሽ አስፍሮ አስኮብልሎሽ

በባዶ ሜዳ ላይ ይሄው አንጓሎ ጣለሽ !

ተስፋ `ያሉ ሚሉት ካንቺው ጋር ተጣብቶሽ

ከአንቺው ተወልዶ

አንቺን አስጨንቆ በምጥ አሰቃይቶ

የነገን ላትኖሪ በነገ ተስፋ ነገን አሳይቶሽ

ተስፋ

ይህ ጽሁፍ የተጻፈው ለሜሮን አባተ ለጻፈችው የግጥም ጽሁፍ መልስ ስለሆነ እሱዋን እንድጽፍ ስላደረገችኝ አመስግኑልኝ !

Previous Story

‹‹99.9% አሰልጣኞች የባርሴሎናን አጨዋወት ለመቅዳት እየጣሩ ነው›› ሉዊስ ሴዛር ሜኖቲ

Next Story

ለእማምዬ

Go toTop