የአስራ አምስት ቀን ህፃን! – በላይነህ አባተ

June 30, 2022

ንፁህ የአማራ ደም ወለጋ ተንጣሎ፣
ጠራርጎ ሊወስደው ዓባይ መጣ ደሞ፣
የተከሉት ችግኝ ስላልዋጠው መጦ፡፡

የደም ጅረት ሲፈስ ፀጥና እረጭ ያሉ፣
የዓባይ ጎርፍ ሲባል መብረቅ ይሆናሉ፡፡

የአስከሬን ተራራን ተመጤፍ ያልጣፉ፣
ምሁር ተብዮዎች ግድብ ይዘክራሉ፡፡

የአስራ አምስት ቀን ህፃን ተደፍታ ስታለቅስ፣
ተናቶች ታያቶች የሬሳ ክምር ውስጥ፣
ምኑን ሰው ሆንና ቆመን የምንሄድ፡፡

ኧረ ተው የሰው ልጅ በሰውነት ቀጥል፣
ተበግ መንጋ አትውረድ በአባይ በመደለል፡፡

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)
ሰኔ ሁለት ሺ አስራ አራት ዓ.ም.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የኢትዮ ሱዳን የድንበር ፍጥጫ ወዴት?

Next Story

የአማራ ክልል መንግስት ተማሪዎችን ሰልፍ ከለከለ «ተማሪዎች ሰልፎች እንዳያደረጉ ለምን ተከለከሉ?» – ዓለምነው መኮንን

Go toTop