ይነበብ «ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም» የ 6 ዓመቷ ህፃን ከወለጋ

June 24, 2022
” ራሴን በተረፈረፉ ሬሳዎች ውስጥ አገኘሁት። ካንገቴ ቀና ስል አንዲት ህጻን (በግምት 6አመት) በ6ታጣቂዎች ተከባለች። እኔ እዛው አጠገባቸው ብሆንም ከተረፈረፈው ሬሳ እንደ አንዱ ስለቆጠሩኝ አላስተዋሉኝም።
ህጻኗን ባማርኛ ያናግሯታል፤ ከዛ ሁሉም ባንዴ ድምጻቸው የገደል ማሚቶ እስኪያስተጋባ ይስቃሉ። በመጨረሻ ህጻኗ ጮክ ብላ ይሄንን ስትል ሰማኋት
“ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም”።
ቀጥሎ የሰማሁት ድምጽ የጥይት እሩምታ ነበር። ለማየት በሚያሣሣ ገላዋ ላይ እሽቅድምድም በሚመስል መልኩ ሁሉም የጥይት አረር አዘነቡባት። ሞታ እንኳን የሚረኩ አይመስሉም ነበር።
ነብሴን ለማትረፍ ከነ ሲቃየ ዝም አልኩ። ከሁሉም ነብሴ ትበልጥብኝ ነበር። ማክሰኞ ህጻኗ የሞተችበት ቦታ ተሰብስበን ሄደን ነበር፤ የለችም፣ ካሣደገኝ አጎቴ ሞት በላይ እስካሁን የምትጠዘጥዘኝ ህጻን!
አፈሩ ይቅለልሽ»
Melat Dawit

Leave a Reply

Your email address will not be published.

ኮሚሽነር ሚሸል ባሽሌ
Previous Story

በምዕራብ ወለጋው ጥቃት ወቅት ታግተው የተወሰዱ ሰዎች እንዳሉ ተገለጸ

Next Story

“የቀበሌው አስተዳዳሪ እኮ ከላይ በተላለፈልኝ ትዕዛዝ ጭፍጨፋውን አስፈጽሜያለሁ አለ ወላሂ” – የቶሌ ቀበሌ ነዋሪ

Go toTop