![](http://amharic-zehabesha.com/wp-content/uploads/2022/05/Tefera-Mano-.jpg)
“ትናንት ረፋዱ ላይ ከአቶ ዩሐንስ ቧያለው ጋር ቀጠሮ እንዳለውና እርሱን ለማግኘት እንደሚሄድ ነግሮኝ ነበር ከቤት የወጣሁት” ያሉት ወ/ሮ መነን “ሁሌ ስብሰባ ወይም ሌላ ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ ጉዳይ ሲኖረው ስልክ ደውሎ ወይም በአጭር የጽሑፍ መልዕክት ያለበትን ሁኔታ ያሳውቅ ነበት ትናንት ግን ይህን አላደረገም። ሁኔታው አላምር ሲለኝ ስልኬን አንስቼ ደጋግሜ ደወልኩ ስልኩ አይነሳም አቶ ዩሐንስ ጋር ደወልኩ እስከ 10:30 ድረስ አብረው እንደነበሩና ወደ መኪናው አስገብቶት እንደተለያዩ ነገረኝ ማታም የቅርብ ዘመዶቻችን ጋር ስደዋውል አየሁት የሚል ሰው አላገኘሁም” ብለዋል።
ዛሬ ጠዋት ፌዴራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና ቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ቢሄዱም ሊያገኟቸው እንዳልቻሉና በኋላም ወደ ብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ ሲሄዱ በነገው ዕለት ወረቀት ፅፈው ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ እንደተነገራቸው ገልፀዋል።
VOA
ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ
\