የብልጽግና ፓርቲ ኮንግረስ አብይ አህመድን ፕሬዝዳንትአድርጎ መረጠ

March 12, 2022

አንደኛ ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኘው ብልጽግና ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ፕሬዝዳንት አቶ ደመቀ መኮንን እና አቶ አደም ፋራህን ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።
አንደኛ ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኘው ብልጽግና የፓርቲውን ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ምርጫ እያካሄደ ነው።
በዚህም መሠረት
ለፕሬዝዳንትነት በሲዳማ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ የተጠቆሙት
ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ናቸው።
በጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ዑሞድ ኡጅሉ ለምክትል ፕሬዝዳንትነት የተጠቆሙት
አቶ ተመስገን ጥሩነህ ናቸው።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አሻድሊ ሀሰን ለምክትል ፕሬዝዳንትነት የተጠቆሙት
አቶ አደም ፋራህ ናቸው።
በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ለምክትል ፕሬዝዳንትነት የተጠቆሙት
አቶ ደመቀ መኮንን ናቸው።
በአሁኑ ሰአት ለጉባኤተኛው ድምጽ መስጫ ወረቀት እየተሰጠ ነው።
ውጤቱን ይዘን እንመለሳለን።
(ኢ.ፕ.ድ)

ሀሃሳብ እና አስተያትዎን ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ፅንፈኝነት ሰላምንም ሆነ ፍትህን እውን ሊያደርግ አይችልም!!!

Next Story

እንደ መሪዎቻችን አሳድረን፤ የሕዝብ ጸሎት – ያሬድ ሃይለማሪያም

Go toTop