ከድልድይ ላይ ራሷን በመወርወር ለመግደል ስትሞክር የነበረችው ወጣት ማን ትሆን?

February 20, 2014

ከዳዊት ሰለሞን

በርብርብ የተረፈችው ወጣት

ትናንት ከሰዓት አካባቢ አራት ኪሎ ለመንገደኞች መሸጋገሪያ ተብሎ በተሰራ ድልድይ ላይ የወጣች በሃያዎቹ መጨረሻ አካባቢ የምትገመት ሴት ራሷን ወደ መኪና መንገዱ ለመወርወር በምትዘጋጅበት ወቅት በአካባቢው የተገኙ ሰዎች ባደረጉት ርብርብ አደጋ ሳይደርስባት ለመትረፍ በቅታለች፡፡
ወጣቷን ለማትረፍ ሁለት የእሳት አደጋ መኪኖች ብዛት ያላቸው ፖሊሶች በስፍራው ተገኝተው የነበሩ ቢሆንም ወጣቷ ‹‹ሙስሊሞችን እወዳለሁ እነርሱን ጥሩልኝ››በማለቷ ሁለት ሙስሊም የሆኑ ሴቶች ቀርበው አነጋግረዋታል፡፡ በዚህ ቅጽበትም ሰዎች ቀርበዋት ይዘዋታል፡፡ ወጣቷን ለዚህ ውሳኔ ያበቃት ምን ይሆን?በቅርቡ ከሳኡዲ የተመለሰች ስደተኛ ትሆን? በስፍራው የነበሩ ሰዎች ይህን መሰል ጥያቄዎች እንድትመልስላቸው ይፈልጉ የነበረ ቢሆንም ፖሊሶች አጣድፈው ወስደዋታል፡፡የት አድርሰዋት ይሆን?

Previous Story

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ “የረዳት አብራሪው አኩሪ ገድል የኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃ እስኪወጣ ይቀጥላል” አለ

Next Story

Sport: ሁለቱ የቸልሲ ምርጦች፦ ኤዲን ሃዛርድ እና ኔማኒያ ማቲች

Go toTop