ዓለምአቀፍ ረጂ ድርጅቶች በጦርነት ቀጠና ላሉ ወገኖች እርዳታ ለማቅረብ ከክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ያደረጉ ቢሆንም እስካሁን ግን ለሕዝቡ ርዳታ አለመስጠታቸዉን አቶ ዘላለም አስታዉቀዋል።
አስቸኳይ ርዳታ የሚሻዉ 6 ሚሊዮን ሕዝብ እርዳታ ባለማግኘቱ ሕብረተሰቡ ከተጋረጠበት አደጋ በራሱ ትግል ሊወጣ እንደሚገባ ኮሚሽነር ዘላለም መምከራቸዉን የባሕርዳሩ ወኪላችን የዓለምነው መኮንን ዘገቧል።
ይህን የዘገበው DW ከሁለት ቀናት በፊት ። ሌሎችም ሚዲያዎች ዘግበውታል።
የምጽፈው ይነበቧችኋል ? 6 ሚሊየን ለረሃብ ተጋልጧል ነው’ኮ የሚሉት ።
ታዲያ ይሄን እያዩ እየሰሙ ዝም ይባላል ወይ ?
መላ አይፈለግም ወይ ?
አይቶ እንዳላየስ ይታለፋል ወይ ?
ሰበር ዜና ተያዘ ተለቀቀ እየተባለ ህዝብ እያለቀ ዝም ይባላል ወይ ?
ዜናው ከ 4 ቀን በፊት የወጣ ነው። ሰበር ዜና ያልኳችሁ ሰበር ዜና ካልተባልን የወገኖቻችን ያሉበትን መረዳት ስላቃተን ነው ።
Via abdurahim ahmed