ለአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች፤
*****
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ የብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በአማራዎች ላይ እየተፈፀመ ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለማውገዝ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱ ይታወቃል።
በጠራው ሰልፍና ከሰልፉ ጋር ተያይዞ በተፈጠሩ ጉዳዮች ዙሪያ ብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚው ዛሬ ማምሻውን እስከ ምሽቱ 5:00 ድረስ ውይይት ያደረገ ሲሆን አብን ጠርቶት የነበረውን ሰልፍ በመንግስት አምባገነናዊ ተግባር ሰልፉን አስተባብሮ በተቋማዊ ማዕከላዊነት ለመምራት ባለመቻሉ መሰረዙን ይገልፃል።
ስለሆነም የንቅናቄያችን አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች አብን ሰልፉን የሰረዘ መሆኑን አውቃችሁ ሰልፎችን ከማስተባበርና ከመምራት እንድትቆጠቡ እያሳወቅን ቀጣይ የአብን የትግል አካሄዶችን በተመለከተ በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል።
አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፣ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ!