Zehabesha Newspaper: ዘ-ሐበሻ በቁጥር 56 ዕትሟ ምን ይዛለች? (PDF)

October 19, 2013

ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ በቁጥር 56 ዕትሟ በውስጧ የያዘቻቸውን ቁምነገሮች እናስቃኛችሁና ለማንበብ ፎቶ ግራፉ ላይ ይጫኑ።
ያው ጋዜጣችን መሠረቷ ሚኒሶታ ላይ በመሆኑ በፊት ገጾቻችን በሚኒሶታ እየተካሄዱ ያሉው ወቅታዊ ሁኔታዎችን ዘግበናል።
– በሚኒሶታ ኦክቶበር 27 አዳዲስ የኮሜዲ ሥራዎችን ይዘው የሚመጡት ክበበው ገዳ፣ መስከረም በቀለና ት ዕግስት ንጋቱ ““ወደሚኒሶታ የምንመጣው አዳዲስ ቀልዶችንና ድራማዎችን ይዘን ነው” ብለዋል። በተጨማሪም መስከረም በቀለ “- “ከሌላው ቦታ በተለየ የሚኒሶታ ሕዝብ ለኮሜዲዎች በጣም እንደሚስቅ ተረድተናል” – ይለናል ዘገባውን ከውስጥ እንመልከተው።
– በሚኒሶታ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ ከ3 ወር በፊት 11 አባላት ብቻ እንዳሉት ከተዘገበ በኋላ ሕዝቡ በገፍ እየተመዘገበ ነው… የአባላት ቁጥር 254 ደርሷል፤ በሚኒሶታ ኢትዮጵያዊ አንድነት እያየለ መጥቷል… ዘገባውን ይመልከቱት..
– የፕ/ር አልማርያም አዲስ ጽሑፍ የቁጥር 56 ዕትማችን አካል ነው፦
* “ለአፍሪካ ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች ፍትሕ አይቀሬ ናት” ይሉናል ፕሮፌሰሩ – ያንብቡት።
– ከሚኒሶታ ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጋር በመተባበርም የማህበረሰብ ጤና ትምህርት በስትሮክ በሽታ ዙሪያ አንድ ዘገባ ይዘናል
– በከተማችን በሚገኙ የማህበረ ቅዱሳን አባላትና ደጋፊዎች ጥያቄ መሠረት በዌብሳታችን ላይ አውጥተነው የነበረው የተመስገን ደሳለኝ “ቀጣዩ የኢሕ አዴግ ኢላማ ማህበረ ቅዱሳን?” የሚለው ዘገባንም ይዘናል
– በእንመካከር አምድ የ4 አንባቢያን ጥያቄ በዶ/ሮች ምላሽ አግኝተዋል፡
* ጓደኞቼ መጥፎ ሽታ ትሸተናለህ ይሉኛል፣ ሽታው ከየት የመጣ ነው?
* ራሴን ለማሻሻል በተደጋጋሚ እቅድ አወጣለሁ፤ ነገር ግን አልተገብረውም፤ ምን ትመክሩኛላችሁ?
* የሴት ጡት አለኝ ምንድን ነው ጉዱ?
* ‹‹የቆዳ ሽፍታና አስም ምን አገናኛቸው? ልጄም እንደኔ የአስም በሽተኛ ይሆንብኝ ይሆን?›› – ለነዚህ ጥያቄዎች የተሰጡ ምላሾች ከጋዜጣችን ውስጥ ተካቷል።
– የኛ ማህበረሰብ በአሜሪካ ጥቅሙን በደንብ ያልተረዳው የሕይወት ኢንሹራንስ (Life Insurance) – በመብት አምዳችን ላይ የተሰተናገደ
– ለወሩ ታላቅ ዜና አምዳችን የጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋን “ፈጠራ የሚመስሉ እውነታዎች” የሚለውን ትንታኔ መርጠናል””
– በጥበብ አምዳችን የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ “ለኛ ደበበ እሸቱ የምንጊዜውም ምርጥ አርቲስታችን ነው” ሲሉ ያቀረቡት ወቅታዊ ጽሁፍ ተይዟል።
– ከወር ወር ሕዝብ በጉጉት በሚጠብቀው የጤና ገጾቻችን 4 ጉዳዮችን ይዘናል
* ዘ-ሐበሻና የሚኒሶታ የጤና ቢሮ በመተባበር በወቅታዊው የጉንፋን በሽታ ዙሪያ አንድ መረጃ ይዘናል
* አትክልት ተመጋቢ መሆን የእንስሳት ተዋፅኦዎችን ይተካል?
* የአስም ህክምናዎችና መድሃኒቶች በቀድሞዎቹ እና በአዳዲስ ጥናቶች ውስጥ
* የአጥንት ነገር! – አጥንቶቻችን ስንት ናቸው? – የአጥንት ስራ ምንድነው? – አጥንት ሲሰበር እንዴት ይኮናል?
– በሳይኮሎጂ አምዶቻችን 2 ጉዳዮችን በዚህ ወር እትማችን ይዘናል
* ሴት ልጅ እንዳፈቀረችህ ማረጋገጥ የምትችልባቸው 10 መንገዶች
* ላፈቀርካት ሴት ያለህን የፍቅር ስሜት እንዴት መግለፅ ትችላለህ?
– በስፖርት አምዳችን 3 ጉዳዮች ተይዘዋል።
* ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ሰሞኑን በድረ ገጹ ያሰፈረው “ናይጄሪያ እኛን፤ እኛ ደግሞ ታሪካችንን አሸንፈናል” የሚለውን ጽሁፍ ለጋዜጣችን አንባቢዎች አካፍለናል
* አርሴን ቬንገርን ወደወጣትነታቸው የመለሰው ፍላሚኒ
* የሚኒሶታው ቫይኪንግ በዚህ ሲዝን
– በወንጀልና ምርመራ አምዳችን ላይ ባሌ ውስጥ ስለተፈጸመ የግድያ ታሪክ የሚያወጋ ጽሁፍ ይዘናል
ምን ይሄ ብቻ?….. በቁጥር 56 እትማችን ብዙ ነግሮች ከማስታወቂያዎች ጋር ታጅበው ቀርበዋል ያንብቡ፤ ያካፍሉ።

Previous Story

በመንዝ ከፍተኛ ረሃብ ተከስቷል

Next Story

በዘንድው ሃጅ ጸሎት የተወገዱት ሰው ሰራሽ አደጋዎች !

Go toTop