እነ ሳሞራ የኑስ አዲስ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሊከፍቱ ነው

October 26, 2016

ከሙሉቀን ተስፋው

አዲሱ የራናይሰንስ ኔትወርክ ቴሌቪዥን፤ በሳሞራ የኑስ ከፍተኛ ሸር ሆልደርነት እና በአፍቃሪ ኢህአዴግ ዲያስፖራዎች ትብብር ሊቋቋም መሆኑን ሰማን።
ይህ የወያኔን ከፍተኛ ባለስልጣናት የገንዘብ እና ፈቃድ ድጋፍ ያገኝው የቴሌቪዥን ጣቢያ ሌላው ድብቁ በዓመት ኢቢሲ ሳይሰራ የሚያግብሰውን 112 ሚልየን ብር ገቢ ለመንጠቅ ያለመ ነው፡፡

ሌላው የፕሮፓጋንዳ ጣቢያ በአንድ ጥያቄ ከብሮድካስት ባለስልጣን ፈቃድ ያገኝ ሲሆን፡ አንዳንድ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን ከገበያ ለማስወጣት እና ስልታዊ የወያኔ አላማን ለማራመድ የተነደፈ እቅድ ነው፡፡፡

ወያኔዎች በዐማራ ስም አዲስ የቴሌቪዥን ጣቢያ በመያዝ መከፋፈል እና መረጃ መቋጣጠር ድብቁ አዲሱ አጀንዳቸው እንደሆነም ሰምተናል።

Previous Story

በተለይ ለኦሮሞ ልሂቃን የተላከ ማስታወሻ (ከነፃነት ዘለቀ)

Next Story

በተስፋ መቁረጥ ኦነግ ሲጋለጥ

Go toTop