አብርሃ ደስታ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው። የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ክለላ ሊፈርሙ ከተወሰዱ ኮሚቴ አባላት አብዛኞቹ ለመፈረም ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ
የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ክለላ ሊፈርሙ ከተወሰዱ ኮሚቴ አባላት አብዛኞቹ ለመፈረም ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ። ዓርብ ጧት ወደ ሱዳን ድንበር አከባቢ በመንግስት አካላት የተወሰዱ ከማይካድራና በረከት ከተሞች የተውጣጡ የድንበር ፈራሚ ኮሚቴ አባላት የሀገር ድንበር መፈረም ከዓቅማችን በላይ ነው በሚል ምክንያት ለመፈረም ስላልፈቀዱ እነሱን ለማሳመን በሚል ምክንያት እዛው በረኻ (ኢትዮሱዳን ድንበር) አሳድሯቸዋል። ከትናንት ማታ ጀምሮ ግን የስልክ ግንኙነት ተቋርጣል። የሆነውን ተከታትዬ እዘግባለሁ ሲል አብርሃ ቃል ገብቷል።