“ትውልድና ሃገር እየገደሉ የተከበሩ መባል የለም!”

April 6, 2022
ዜና ቲዩብ አንድ መምህርን ጠቅሶ እንደዘገበው በአንድ ዩኒቨርሲቲ ከመምህራንና አመራሮች ጋር በተደረገ ስብሰባ ላይ የት/ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተገኝተዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ሚ/ሩን ወደ መድረክ ሲጋብዟቸው “የተከበሩ…” ይሏቸዋል። ፕ/ሩም ንግግራቸውን ሲጀምሩ “ማንም የተከበረ የለም። ትውልድና ሃገር እየገደሉ የተከበሩ መባል የለም። ምናል መስዋዕትነት ከፍለን መጪውን ትውልድ ከሞት የታደግን ከሆነ እነሱ የተከበሩ ሊሉን ይችላሉ” ይላሉ። ቀጥለውም የትምህርት ስርዓቱን መበስበስ ምክንያቶች በዝርዝር ከተናገሩ በኋላ የዩኒቨርሲቲው መምህራን የመፍትሄ ሃሳብ እንዲያቀርቡ ጠየቁ።
ከቀረቡት ሃሳቦች ውስጥ 99% የቤት መስሪያ ቦታ እና የመኪና መግዣ ብድር ጥያቄ ነበር። ሚኒስትሩም ይህን ሲሰሙ በብስጭት ዩኒቨርሲቲውን ጥለው ሄዱ። ይላል ደረጀ ሃ/ወልድ በዘገባው።

Gedewon Teka Abegaz

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በኢትዮጵያ 26.2 ሚሊዮን ህዝብ የስብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ይፈልጋል፣በድርቁ 1.7 ሚሊዮን እንሰሳት ሞተዋል!

Next Story

በአዲስ አበባና በኦሮሞ ክልል አዋሳኝ አካባቢ እየተካሄደ ያለው የመሬት ዕደላ ብዥታ ፈጥሯል

Go toTop