Ad ends in 17s የአማራ ልዩ ሀይል ተከዜ ብርጌድ ደመወዝና ሎጂስቲክስ መቋረጡ ተገለፀ

March 16, 2022
ተወርዋሪው የአማራ ልዩ ኃልል ተከዜ ብርጌድ 3 ወር ሙሉ ደሞዝ መቋረጡንና እና ሎጅስቲክ አለመቅረቡ ተገለፀ። በአማራ ልዩ ሃይል ላይ የታቀደው ሴራ እጅግ በጣም ከባድ በመሆኑ የልዩ ሃይል አመራር እና አባላት ይሄን ጉዳይ ብስለት በተሞላበት መልኩ በመያዝ ታሪካዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸውም ተገልጿል።
በዚሁ ምክንያት ከባህር ዳር ጎንደር ዛሬ ከጧት ጀምሮ ትራንስፖርት ተቋርጦ ውሏል::
የአማራ ልዩ ሀይል ከተለያዩ ግንባሮች በክልሉ መንግስት በቂ ድጋፎች እየተደረገላቸው ባለመሆኑ ሰላም የማስከበር ስራ አንሰራም በማለት ለክልሉ መንግስት ቅሬታ ለማቅረብ ወደ ባህር ዳር እየተጓዙ ባለበት ወቅት አዲስ ዘመን አካባቢ ከመንግስት አካላት በቀረበላቸው ጉዳዩን በውይይት እንፍታው የሚል ጥያቄ መሰረት ውይይት እያካሄዱ በመሆኑ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደተቋረጠ የአዲስ ዘመን ከተማ ብልጽግና ሀላፊ አቶ ምስጋናው ማስረሻ ለአሻራ ሚዲያገልጸዋል::
ሀላፊው ለትራንስፖርት መቋረጡ በምክንያትነት ያነሱት ለቅሬታ ከመጡ የልዩ ሃይል አባላት ጋር የሚደረገው ውይይት አስፓልት ላይ በመሆኑ ነው የሚል ምላሽ ሰጠዋል::
ውይይቱ ለሁለት ቀን ያክል አስፓልት ላይ እየተካሄድ መሆኑን በመግለጽ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ተኩስ ተከፈተ የሚባለው ወሬ ውሸት ነው ሲሉም ተናግረዋል ::
አሻራ ሚዲያ 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በኢትዮጵያ እና ህዝብ ላይ ለደረሰዉ እና ለሚደርሰዉ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት የሚወስደዉ  ማን ነዉ ? -ማላጂ

Next Story

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አፈናና የተማሪና ወላጅ ተስፋ ያጨለመው ውሳኔ | Hiber Radio

Go toTop