ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር ተያይዞ ከተለያዩ የሽብር ቡድኖች ጋር ግንኙነት አላቸው ተብሎ የተጠረጠሩ ሰዎችን የጸጥታ አካላት በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ይታወሳል፡፡
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሠ ቱሉ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በጸጥታ አካላት ተጠርጥረው ከታሰሩት ውስጥ የጥፋት ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆነና መንግስት ከጥፋታቸው ተገቢውን ትምህርት ወስደዋል መንግስት ጉዳዮን በሆደ ሰፊነት አይቶ የለያቸው በርካታ ሰዎች በይቅርታ እንዲለቀቁ አድርጓል ብለዋል፡፡
የቀሩትም እንደ ሁኔታው የጥፋት ደረጃቸው እየታየ ቀጠይ የሚለቀቁ እንደሚሆን ገልጸው፤ቁልፍ የችግሩ ተዋንያን የሆኑት ደግሞ ጉዳያቸው ተጣርቶ ለፍርድ ቤት የሚቀርብ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡
የመንግስት ዓላማ አስተማማኝ፣ ዘላቂ ሠላም አስፍኖ የህግ የበላይነት እንዲረጋጋጥ ማስቻል ነው ያሉት ዶክተር ለገሠ፤ ይህንን የሚገዳዳር ማናቸውን እንቅስቃሴዎች ከህግ ተጠያቂነት አያመልጥም ብለዋል፡፡
ሕዝቡም እስካሁን የሚያደርገውን ድጋፉን እንደ ወትሮው ሁሉ አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡
በጌትነት ምህረቴ (ኢ ፕ ድ)