ይድረስ ለሚኒሶታ መድኃኔዓለም ምዕመናን፡ የተከፋፈሉት አባቶች 1 አስኪሆኑ ድረስ በአስተዳደር ገለልተኝነት ለመቆየት 7 ምክንያቶች

December 13, 2013

ቀን፡ 12-12-13
በሥላሴ ስም አንድ አምላክ አሜን።
ይድረስ ለሚኒሶታ መድኃኔዓለም ምዕመናን
ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተከፋፈሉት አባቶች አንድ አስኪሆኑ ድረስ በአስተዳደር ገለልተኝነት መቆየት ይገባታል!

ምክንያቶች፦
1. የደብራችንን ሰላምና አንድነት ለመጠበቅ ያስችላል።
2. የተከፋፈሉትን አባቶቻችንን ለማቀራረብ በሚካሔደው ጥረት ውስጥ ተሳታፊ ለመሆንና የክርስቲያኖችን ድርሻን ለመወጣት ይጠቅማል።
3. የክርስትና ጠባይ ያልሆኑትን የፖለቲካና የዘረኝነትን ነገር በደብራችን እንዳይኖር ይረዳል።
(ስለአገርና ስለኅዝብ መበደል፣ ስለቤተክርስቲያን ጥቃትና መብት ገፈፋ መናገር ግን ፖለቲካ አይደለም።)
4. በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ በማንኛውም አካል በቤተክርስቲያን ላይ አንዲሁም በአገርና በህዝብ ላይ የሚደርሱ በደሎችን ተቃውሞ ድምጽን በነጻነት ለማሰማት ይረዳል።
5. ከሌሎች ቤተክርስቲያናት ጋር መልካም ግንኙነት እንዲኖርና በሕብረት ለማገልገል ያስችላል።
6. የምእመናንን ቁጥር ለማብዛትና የቤተክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ እድገት ለማምጣት ያስችላል።
7. ወገናዊነት ሳይኖርና ያለህሊና ወቀሳ እምነትን በነጻነት ለመፈጸም ይጠቅማል።

ከዚህ አንፃር በአሁኑ ሰዓት ዘረኝነት፣ አድሎ፣ሙስና፣ወዘተ ወዳለበትና በቀጥታ በመንግስት በሚታዘዝ አስተዳደር ስር እንሁን የሚሉ ክፍሎች ተሳስተዋል። በደብረ ሰላም ዘረኝነት የለም! ለማንም የፖለቲካ ድጋፍ መስጠት የለም!
ስለሆነም ቤተክርስቲያንህን በመንግስት አመራር ስር ለማድረግ የሚሮጡትን ልትቀድማቸው ይገባል!
ለብዙ አመታት ገንዘብህን ፣ጉልበትህን ፣እውቀትህን ፣ጊዜህንና ላብህን አፍስሰህ እዚህ ያደረስከውን የአምልኮ ቤትህን እንዳትቀማ ተነስ።
የችግሩን መንሰኤና መፍትሄ ልቦናቸው እያወቀ አሳልፈው ሊሰጡህ ባሴሩትንም ‘ካህናት’ ላይ ርምጃ ልትወስድ ይገባል።

ለቤተክርስቲያን አንድነት እና ሰላም ከቆሙ ምዕመናን።

Previous Story

Sport: ቀነኒሳ በቀለ በኤደንበርግ አገር አቋራጭ ውድድር ላይ እንደሚሮጥ ታወቀ

Next Story

በአዲስ አበባ ከ600 በላይ አባዎራዎች ቤታቸውን በ3 ቀናት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ ቀጭን ትዕዛዝ ተላለፈ

Go toTop