በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ፤ የአጋዚ ጦር አካባቢውን ወሮታል

May 10, 2014

አሁን ለዘ-ሐበሻ በደረሰ መረጃ መሠረት፦

በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ የአዲስ አበባን አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወምና ሰሞኑን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በአጋዚ ወታደሮች የተገደሉ ወገኖችን ለማሰብና ገዳዮች ለፍርድ እንዲቀርቡ እየጠየቁ ያሉ ሰዎች አደባባይ የወጡ ሲሆን ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ባሉበት ወቅት በአጋዚ እና በፌደራል ፖሊስ መከበባቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ።

የአጋዚ ጦር በጊምቢ ወረዳ የተከሰተውን የተቃውሞ ሰልፍ ለማብረድ የኃይል እርምጃ እንደወሰደ የገለጹት የዘ-ሐበሻ ሰዎች ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ ያረጋገጥነው ነገር የለም ብለዋል።

ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እንመለሳለን።

Previous Story

ምናባዊ ቃለምልልስ ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር

Next Story

የሄንሪ ቀመር በአንፊልድ ሊቨርፑል (ልዩ ትንታኔ)

Go toTop