አዎ! የዛሬው ወለጋ ኦሮሞ ኢትዮጵያን ከመውረሩ በፊት የጥንት ስሙ ቢዛሞ ይባል ነበር! – አቻምየለህ ታምሩ

April 26, 2022
ከሰሞኑ በሰጠሁት አንድ ቃለ ምልልስ ላይ «ወለጋ ከኦሮሞ ወረራ በፊት የጥንት ስሙ ቢዛሞ ይባል ነበር» በማለት የተናገርሁትን አንድ ወዳጄ «ይህ የደብተራ ታሪክ ነው፤ ማስረጃ ልታቀርብ አትችልም» የሚል ትችት ሰንዝሮ ነበር። «ማስረጃ ልታቀርብ አትችልም» ብሎ ማስረጃ እንደመዝ የገፋፋኝን ወዳጄን ስለትችቱ እያመሰገንሁ ማስረጃዬን እነሆ ብያለሁ።
ወለጋ ከኦሮሞ ወረራ በፊት የጥንት ስሙ ቢዛሞ ይባል እንደነበር የጻፉት ትምህርት የላቸው ተብለው ባላዋቂዎች የሚሰደቡት «ደብተራ» የታሪክ ጸሐፊዎች ሳይሆኑ የሎንዶን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ምሩቅ ኦሮሞው አቶ ይልማ ደሬሳ ናቸው። አቶ ይልማ ደሬሳ ከጥሊያን ወረራ በፊት ከሎንዶን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ በዲግሪ የተመረቁ ሲሆኑ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ለብዙ ዓመታት የገንዘብ ሚኒስትር ነበሩ።
አቶ ይልማ የወለጋው ባላባት የደጃዝማች በከሬ ጎዳና ኦሞ ፋሮ ሲኒካ ኘአ ዶሮ የልጅ ልጅ ናቸው። የአቶ ይልማ አያት ደጃዝማች አመንቴ በከሬ ይባላሉ። የደጃዝማች አመንቴ በከሬ ልጅ ደግሞ የአቶ ይልማ ደሬሳ አባት ብላታ ደሬሳ አመንቴ ናቸው።
አቶ ይልማ ደሬሳ በ1959 ዓ.ም. «የኢትዮጵያ ታሪክ በአሥራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን» በሚል ባሳተሙት የታሪክ ጥናታቸው የዛሬው ወለጋ በ17ኛው መቶ ክፍለ በኦሮሞ ተወርቶ ስሙ ወደ ወለጋ ከመቀየሩ በፊት ጥንተ ስሙ ቢዛሞ ይባል ነበር። በግዛቱም አማራ፣ ጋፋትና እናርያ የሚባሉ ነገዶች ይኖሩበት ነበር። የቢዛሞ ግዛት ከዐፄ ዐምደ ጽዮን ጀምሮ የኢትዮጵያ አካል እንደነበር በዐፄ ዐምደ ጽዮን ታሪከ ነገሥትተ መዝግቦ ይገኛል።
ኦሮሞ በተለይም የሜጫ ኦሮሞ አካባቢውን ወርሮ ከያዘው በኋላ ግን ነባር ነገዶች ጠፍተውና ማንነታቸው በኦሮሞ ተቀይሮ ታሪካዊው የቢዛሞ ግዛት የስም ለውጥ አድርጎ ወለጋ ለመሆን በቅቷል። ( ምንጭ፡ ይልማ ደሬሳ (1959)፥ የኢትዮጵያ ታሪክ በአሥራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን፥ገጽ 17)
በአቶ ይልማ መጽሐፍ ውስጥ የሚገኘው ሙሉ ታሪክ እነሆ!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ጎንደር ከተማ ላይ በግፍ የተገደሉት ወንድሞች ቁጥር ሶስት ደርሷል

Next Story

ኋላ-ቀር አስተሳሰብ ባላቸውና በአረመኔዎች የሚመራ ምስኪን ህዝብና አገር! – ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)

Go toTop