ካዛንቺስ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት የአንድነት አመራሮችና ጋዜጠኛ ፍ/ቤት ቀርበው የ11 ቀን ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፡፡

May 2, 2014

የአንድነት ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚና የአዲስ አበባ ሰብሳቢ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን ፣አቶ ዘላለም ደበበ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል እና የፍኖተ ነፃነት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ እንዲሁም የመኪናው ሹፌር ነፃነት ዘገየ ሜክሲኮ በሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዛሬ ቀርበው ሰላማዊ ሰልፍ እንጂ ለመኪና ቅስቀሳ አልተፈቀደም ፤ ቅስቀሳውን የደረጉት የተከለከለ ቦታ ነው ድርጊቱም ያደረጉት ሆነ ብለው ብጥብጥና ሁከት ለማስነሳት ነው፣ የዋስትና ቢሰጣቸው ከግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆን ሁከት ያስነሳሉ በማለት የዋስትና መብታቸውን ተከልክለው የ11 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡

Previous Story

አንድነት ፓርቲ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ “የእሪታ ቀን” በሚል ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ይቀላቀሉ! (ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር)

Next Story

ኢቲቪ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እሁድ የሚያደርገውን ሰላማዊ ሰልፍ ማስታወቂያ አላስተናግድም አለ፡፡

Go toTop