ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጃማ ደጎሎ ግንባር ባደረጉት ገለፃ የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ወደ ደሴ የሚቃረብበትን መንገድም ይይዛል ብለዋል፡፡
በደጎሎ ግንባር ስልታዊ ኦፕሬሽኖች እየተደረጉ ሲሆን በዚህም ሰሜን ሸዋ የገባው የጠላት ኃይል እንዳይወጣ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡
እንደ ጋሸና ባሉ ድል በተገኘባቸው አካባቢዎች ይዞታን የበለጠ የማስፋት ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
‹‹አሁን ላይ ጠላት ፈርሷል፤ ተሸንፏል›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝቡ ጋር ሆኖ ጠላትን የመልቀም፣ የዘረፈውን ንብረትና ትጥቅ የማስቀረትና ጠላት በቡድን ሆኖ የማይወጣበትን አግባብ የመፍጠር ሥራ ነው እየተሰራ ያለው ብለዋል፡፡
ኅዳር 23/2014 (ዋልታ)