“በጎንደር ከተማ የተከሰተውን ችግር መሰረት በማድረግ ከሃይማኖት አስተምህሮ በተቃረነ መንገድ ጥላቻን የሚያስፋፉ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል” – የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ

April 28, 2022
በጎንደር ከተማ የተከሰተውን ችግር መሰረት በማድረግ ከሃይማኖት አስተምህሮ በተቃረነ መንገድ ጥላቻን የሚያስፋፉ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከትናንት በስቲያ በጎንደር ከተማ የተከሰተውን ግጭት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
መግለጫውን የሰጡት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሃፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ እንደገለጹት፣ የጐንደር ከተማ በሁሉም የሃይማኖት ተቋማት በመቻቻል፣ በመከባበር የሚታወቅ ከተማ ነው። ይሁን እንጂ ሰሞኑን ከሁሉም የሃይማኖት አስተምህሮ ውጭ የሆነ ድርጊት ተፈጥሯል።
የተፈጠረውን ችግር ምክንያት በማድረግ በተለያዩ የማህበራዊ ገጾች ከእምነቱ አስተምህሮ በተቃረነ መንገድ እያራገቡ ለተጨማሪ ጥፋት የሚቀሰቅሱ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ብለዋል።
የተፈጠረው ችግር ከየትኛውም የሃይማኖት አስተምህሮ ያፈነገጠ በመሆኑ ጉባኤው አውግዟል።
ጠቅላይ ጸሃፊው በመግለጫቸው፣ የተፈጠረውን ችግር የሃይማኖት ግጭት በማስመሰል ሀገር ለማተራመስ በሚሰሩ አካላት ላይ የክልሉ መንግስት የእርምት እርምጃ እንዲወስድም ጉባኤው አሳስቧል።
በሞገስ ተስፋ/(ኢ.ፕ.ድ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ትሕነግ ከአፋር ክልል ሙሉ በሙሉ አለመውጣቱን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ

Next Story

” የነ ጃሥ ዋር “ታላቁ ሤራ ፤ በኃይማኖት ግጭት ፤ ተጀምሯል። – ሲና ዘ ሙሴ  

Go toTop