“ድንገት አመሻሹ ላይ ነው ዕቃችሁን ይዛችሁ ውጡ የተባልነው” የባልደራስ አመራር

January 7, 2022

የባልደራስ ከፍተኛ አመራር የሆኑትና በቂሊንጦ ከአቶ እስክንድር ነጋ ጋር ታስረው የነበሩት የፓርቲው የድርጅት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ቸኮል በዛሬው ዕለት ከምሽቱ 12፡30 አካባቢ የማረሚያ ቤቱ ሠራተኞች ድንገት መጥተው ከማረሚያ ቤቱ እንዲወጡ እንደነገሯቸው አስስረድተዋል።

“ድንገት አመሻሽ ላይ መጥተው ዕቃችሁን ይዛችሁ ውጡ አሉን፤ ያው እቃችንን ይዘን ወጣን። ምንም የምናውቀው ነገር የለም” በማለት አቶ ስንታየሁ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እንደወጡ በስልክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።  አቶ ስንታየሁን በስልክ ባገኘበት ወቅት ከቂሊንጦ ማረሚያ ወጥተው ከአቶ እስክንድር ጋር ከማረሚያ ቤቱ አቅራቢያ ወደሚገኝ ቤተ ክርስቲያን እያመሩ እንደሆነም ገልጸዋል። “በዋናነት የተፈታነው በአምላክ ኃይል ነው፤ እውነት ነው ያሸነፈው፤ የሕዝብ ትግል፣ የሕዝብ እንባ ነው ያሸነፈው” ብለዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የኦሮሞ ህዝብ አዲስ የፖለቲካ ትግል ምዕራፍ!

Next Story

የሕወሓት ወራሪ ኃይል ወደ ወልቃይት 9 ጊዜ መድፍ ተኮሰ።

Go toTop