(ከአዘጋጁ) ትናንት በዋሽንግተን ዲሲ የሳዑዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት የተደረገው ደማቅ የተቃውሞ ሰልፍ የውጭ ሚድያዎችን ሽፋን እያገኘ ነው። በዚህም መሠረት የላቲን ቲቪ ትዕይንተ ሕዝቡን ዘግቦታል። እኛ ኢትዮጵያውያን የሳዑዲ አረቢያ ያሉ ወገኖቻችንን በማስመልከት ሰልፍ ከምንወጣባቸው ምክንያቶች አንዱ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡት መጠየቅም በመሆኑ በላቲን ቲቪ መዘገቡ ትግላችን ሰሚ እያገኘ እንደሆነ ያሳያል። ቪድዮው፦