የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት እስከዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ የተወካዮች ምክር ቤት ያፀደቀውን ህግ ተቃውሟል፡፡ የተቃወመውም በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በአብላጫ ድምፅ የፀደቀውን የአስተዳደር ወሰንና የማንነት ጉዳዮች ኮምሽን ማቋቋሚያ አዋጅን ነው፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=p8iBU5RCUVc&t=50s
የክልሉ ምክር ቤት አዋጁ ‹‹ህገ መንግስቱን ስለሚፃረርና ህገመንግስቱን ስለሚጥስ በሕገመንግስቱ አንቀፅ 9/1 መሰረት በክልሉ ውስጥ እንዳይፈፀምና ወደ ተግባር እንዳይገባ›› የሚል ውሳኔ በትላንትናው እለት በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።
ይህ አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት በፀደቀበት ወቅትም ሁሉም የትግራይ ክልል የምክር ቤቱ አባላት ተቃውሞ ማሰማታቸው ይታወቃል፡፡ ይህ ድርጊት ትግራይ ክልል በፌዴራል መንግስት ለመመራት ፈቃደኛ ለመሆኑን ማሳያ መሆኑን የጠቆሙት የፖለቲካ ታዛቢዎች የህወሀት አመራሮችን የመጨረሻ ትእቢት እንደሚያመላክትም አስረድተውናል፡፡ አንድ ክልል በፌዴራል ስርአቱ ህግ ካልተገዛ ራሱን ከፌዴራል አስተዳደሩ እያገለለ ለመሆኑ ጠቋሚ በመሆኑ ከወዲሁ ሊታሰብበት እንደሚገባ ታዛቢዎቹ ተናግረዋል፡፡ በተወካዮች ምክር ቤት ካለው 547 መቀመጫ ውስጥ የትግራይ ክልል ድርሻ 38 ብቻ በመሆኑ ቀሪዎቹ በሚወስኑት ማናቸውም ውሳኔ የመገዛት ግዴታ አለባቸው፡፡