ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 60 – PDF

February 22, 2014

በሰሜን አሜሪካ ትልቋ የኢትዮጵያ ጋዜጣ ዘ-ሐበሻ እነሆ ቁጥር 60 ለንባብ በቅታለች።
እንደተለመደው በውስጧ የያዘቻቸውን ቁምነገሮች እፍታውን እናጨብጣችሁና ንባቡን ለናንተው እንተወዋለን።

* ዓብይ ትኩረታችን ያደርግነው በአውሮፕላኑ ጠለፋ ዙሪያ ነው። የተለያዩ ጉዳዮች ተዳሰዋል።
– ከአውሮፕላኑ ጠለፋ ባሻገር የፖለቲካ ይዘት አለው
– አውሮፕላኑን የጠለፈው ኃይለመድህን አበራ ተገኝ ማን ነው?
– የሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የዜጎች እኩልነት አለመረጋገጥ፣ በሥራ ቦታ ላይ ነጻነት ማጣት፣ የኢኮኖሚ ችግር፣ የነፃነት እጦት አውሮፕላኑን አስጠለፈው
– የረዳት ፓይለቱ ድርጊት የአፈናው ውጤት?
– የኢትዮጵያ ነገርና – የአብራሪው ጉዳይ የሚሉ ወቅታዊ ዘገባዎችን ይዘናል።
* በወሩ ታላቅ ዜና አምዳችን፡ የቀድሞው አዲስ ነገር ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ “ኢትዮጵያዊነት-”የለህም ይሉኛል፤ እውን የለህም ወይ?” በሚል የፃፈውን ወቅታዊ ትንታኔ ይዘንላችኋል።
* ከሚኒሶታ የጤና ማዕከል ጋር በመተባበር በምናቀርበው አምዳችን ‘ስለ ክትባቶች እና ስለ እርግዝና ሊያውቋቸው የሚገቡ ነገሮች” የሚል ትንታኔ ይዘናል፤ ቢያነቡት ይጠቀማሉ።
* አዲሱን የNYPD (የኒዮርክ ፖሊስ ዲፓርትመንት) ስማርት ካር ውስጡ ምን እንዳለው ሰምተዋል? – ሊያመልጥዎ አይገባም።
* በሕይወት በአሜሪካ አምዳችን፡ ሥራ ፍለጋ ኢንተርኔት ገብቼ ፌስቡክ ላይ ተሰጥቼ እውላለሁ የሚል ትዝብታዊ ጽሁፍ አካተናል።
* ተወዳጁ ድምፃዊ ብርሃኑ ተዘራ (ያምቡሌ) በሚኒሶታ ሥራዎቹን ማርች 15 ያቀርባል
* ዲያቆን ዳንኤል ክብረት “የመረረው አብዮተኛ (ለ1966ቱ አብዮት 40ኛ ዓመት ማስተዋሻ)” በሚል የፃፈው መጣጥፍም የቁጥር 60 ዕትማችን አካል ነው።
በወንጀል ዜና አምዳችን፦
– 3 ልጅ የወለደችለት ሚስቱን በጥርጣሬ የተነሳሕይወቷን አጠፋ
– በአዲስ አበባ ቦሌ አካባቢ የታክሲ ሾፌሩን ተሳፋሪው ገደለው የሚሉ ሁለት ዜናዎችን ይዘናል ትንታኔ አላቸው።
በእንመካከር አምድ 4 ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷቸዋል።
– “ከባለቤቴ ጋር ስምምነት መፍጠር ተሳነኝ፤ እባካችሁ አንድ በሉኝ”
– ከድብርት ለመላቀቅ ወሲብ ማድረግ ቢነገረኝም እርሱም አልረዳኝም
– ጉሮሮዬ ከተዘጋ 10 ዓመት ሆነው
– በዱካክ ተሰቃየሁኝ፤ ምን መፍትሄ አላችሁ? ምላሾቹን ያንብቧቸው፤ ይማሩባቸዋል።
* በጤና አምዳችን 3 ጉዳዮች እንደተለመደው ተካተዋል።
– ፕሮቴስት የወንዶች ብቻ ችግር (ወንዶች ልብ ብላችሁ አንብቡት)
– ትራኮማ እና የዓይን ሞራ ግርዶሽ
– የነስር ነገር – Epistaxis ፦ ለምን ይነስረናል? የሚሉ 3 ምርጥና አስተማሪ ዘገባዎችን አካተናል ያንብቡን።
* በሴቶች አምድ፡ ማስካራ ትጠቀሚያለች? እንግዲያውስ ይህን አንብቢ ትለናለች ሊሊ ሞገስ፤ ያንብቡላት።
* በሳይኮሎጂ አምዳችን፤ ቅናት ለፍቅር ምኑ ነው? የሚል ቆንጆ ዘገባ አለን።
* በስፖርት አምድ እንዳስለመድነው 3 ጉዳዮች አሉን።
– ፍሌቸር በቀን እስከ 30 ጊዜ መጸዳጃ ቤት ይመላለስ ነበር
– ማርቴሳካር፡ ግዙፉ ጀርመናዊ
– ጋሪ ኩክ የማንቸስተር ሲቲው አዳኝ
በዘ-ሐበሻ ቁጥር 60 ላይ እነዚህ ብቻ አልተካተቱም፤ በርከት ያሉ ዘገባዎች ከማስታወቂያዎች ጋር ታጅበው ቀርበዋል። ያንብቡ።

ጋዜጣውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Previous Story

ባሶንዳ በተባለችዉ የሱዳን ጠረፍ ከተማ 77 ኢትዮጵያዉያን ተገድለዋል ተባለ

Next Story

ቦይንግ 767 – እገታ እና እንድምታው – ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

Go toTop