የአንድ የአሜሪካ ዶላር የባንኮች መሸጫ ዋጋም ከ110 ብር ወደ 115 ብር ጨምሯል – ዋዜማ

March 3, 2023

ለቸኮለ! ዓርብ የካቲት 24/2015 ዓ.ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የግል ባንኮች በአሁኑ ወቅት ለአንድ ዶላር የሚያስከፍሉት ኮሚሽን ወደ 65 ብር ማደጉን ዋዜማ ተረድታለች። የአንድ የአሜሪካ ዶላር የባንኮች መሸጫ ዋጋም ከ110 ብር ወደ 115 ብር ጨምሯል። የውጭ ምንዛሬ ግብይቱ የሚፈጸመው፣ በባንክ የውጭ ምንዛሬ ባስቀመጡ ግለሰቦችና በውጭ ምንዛሬ ፈላጊዎች መካከል በደላሎች አገናኝነት ነው። አስመጪዎች አገር ውስጥ በብር ክፍያ ፈጽመው ውጭ አገር ባሉ ሰዎች ለሚፈልጉት ዕቃ በውጭ ምንዛሬ ክፍያ ተፈጽሞላቸው ዕቃ ለማስገባትም፣ ለአንድ ዶላር በተመሳሳይ 105 ብር ይከፍላሉ። ባንኮች የሚሸጡት የውጭ ምንዛሬም ከጥቁር ገበያው ጋር ተመሳሳይ እየሆነ መምጣቱን ዋዜማ ታዝባለች። ብሄራዊ ባንክ ዛሬ ለአንድ ዶላር መሸጫ ያወጣው ዋጋ ግን፣ 54 ብር ከ83 ሳንቲም ነው። ዝርዝሩ- https://bit.ly/3kATBPn

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

EOTC ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና አደስ አበባ ሀገረ ስብከት የተሰጠ መግለጫ

Next Story

ደመቀ መኮንን፣ ደመላሽ ፍኖ እና ዳያስፖራ ፋኖ  

Go toTop