Español

The title is "Le Bon Usage".

በዝግ ችሎት ይሁን/ አይሁን በሚል ከርክር ያስነሳው እና በሚዲያ የምስክሮች ቃል እንዳይዘብ የተከለከለው የእነሀብታሙ፣ አብርሃ …የፍርድ ቤት ዘገባ

June 8, 2015

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

የሺዋስ አሰፋ ከተቀመጠበት አልነሳም አለ!

‹‹ምስክሬ ላይ ዛቻ እና ድብደባ ስለተፈጸመ ምስክርነቱ በዝግ ችሎት ይሁን›› አቃቤ ሕግ
‹‹በማስረጃ ባልተረጋገጠ አቤቱታ ችሎት በዝግ ሊታይ አይገባም›› የተከሳሽ ጠበቆች
‹‹ሞት የሚያስቀጣ ክስ ቀርቦብን ጉዳያችን በአደባባይ መታየት አለበት፤ እናንተ ብቻ አይደላችሁም ፈራጆች…››ዳንኤል ሺበሺ
‹‹ምስክርነቱ በዝግ ችሎት የሚታይ ከሆነ ዛሬውኑ የምትፈርዱብንን ተቀብለን ለመመለስ ዝግጁ ነን›› ሀብታሙ አያሌው
‹‹የአቃቤ ህግን አቤቱታ በማስረጃ ያልተደገፈ በመሆኑ አልተቀበልነውም፤ የምስክሮች ስምና ቃል ግን በሚዲያ እንዳይዘገብ ወስነናል›› ችሎቱ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ዛሬ ሰኔ 01 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በእነዘላለም ወርቅአፈራሁ የክስ መዝገብ የተከከሱ 10 ሰዎች ጉዳይ ታይቶ ነበር፡፡ መዝገቡ የተቀጠረው አቃቤ ህግን ምስክሮች ለማድመጥ እና የአቃቤ ህግን ባቀረባቸው ተጨማሪ አቤቱታዎች ላይ ውሳኔ ለመስጠት መሆኑን ከችሎቱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ተከሰሾች በቀደም ተከተል ስማቸው እየተጠራ ሲቆሙ የሺዋስ አሰፋ ከመቀመጫው አልነሳም ብሎ ነበር፡፡ የቀኝ ዳኛው ተነስ ቢለውም የሺዋስ በሀሳቡ ጸንቶ አልተነሳም፡፡

አቃቤ ህግ ካስመዘገባቸው 15 ምስክሮች መካከል 12ቱን ዛሬ ማቅረብ የቻለ ቢሆንም ‹‹በአንደኛ ምስክር ላይ ዛቻ እና ድብደባ ስለተፈጸመ፣ እንዲሁም የሁሉንም ምስርክሮች ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ምስክርነቱ በዝግ ችሎት ይደረግልን›› ሲሉ አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ አቤቱታቸውን አሰምተው ነበር፡፡

ተከሰሾች 3 ጠበቆች የነበሯቸው በመሆኑ ከ1ኛ-5ኛ ተራ ቁጥር ድረስ የተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ የአቃቤ ሕግን አቤቱታ እንዲህ በማለት ተቃውመዋል፡- ‹‹ችሎት አስተማሪ በመሆኑ በግልጽ ይታይ ዘንድ መርህ ነው፡፡ ችሎት ዝግ የሚሆነው በተለየ መንገድ ነው፡፡ በሕገ-መንግሥቱ ይህንን በተመለከተ ተደንግጓል፡፡ የችሎት ዝግ መሆን ሊፈቀድ ቢችል እንኳን በማስረጃ ተረጋግጦ መሆን ይኖርበታል፡፡ አቃቤ ሕግ ያቀረበው አቤቱታ በማስረጃ ዘርዝሮ የት፣ መቼ፣ እንዴት የሚለውን አላቀረበም፡፡ ችሎት በአቤቱታ ብቻ አይዘጋም፡፡ በማስረጃ ባልተረጋጋጠበት ሁኔታ ፍርድ ቤቱ ሊፈቅድ አይገባምና የአቃቤ ህግ አቤቱታ ውድቅ ይደረግልን፡፡›› የተቀሩት ሁለት ጠበቆችም በተመሳሳይ መልኩ የአቃቤ ህግን አቤቱታ ተቃውመዋል፡፡

የቀድሞ አንድነት አመራር የነበረው አቶ ዳንኤል ሺበሺም እጁን በማውጣት እንደምንም ካስፈቀደ በኋላ፤ ‹‹ሞት የሚያስቀጣ ክስ ቀርቦብን ጉዳያችን በዝግ መታየት የለበትም፡፡ በአደባባይ ሊታይ ይገባል፤ እናንተ ብቻ አይደላችሁም ፈራጆች፤ ሁሉም ይፍረድ፡፡ ሁሉም ይፈርዳል›› ብሏል፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌውም እንዲናገር ጠበቃ ተማም ለዳኞቹ ተናግረው ሀብታሙ ‹‹አቃቤ ህግ ክስ ሲመሰርትብን በዝርዝር የምስክርችን ስም አልገለጸም፡፡ እኛ ዋስትና ተከልልለን በእስር ላይ ነው የምንገኘው፡፡ ምስክሮችን ልናውቅ የምንችልበት ዕድል ዝግ ነበር፡፡ ዛሬ ገና ነው በከፊል ምስክሮችን እዚህ ያየናቸው፡፡ አቃቤ ህግ ‹ምስክሮቼ ዛቻ ደረሰባቸው፣ ተደበደቡ› ካለ ሊጠየቅ የሚገባው እሱ ነው፡፡ ማነው በጀርባ ያለው? እኛ ከእስር ቤት ሆነን እንዴት ብለን ልናስፈራራ እንችላለን? ይሄ ከአየር ላይ የመጣ ፍረጃ ሲሆን የተፈጸመ ነገር ካለ በግልጽ ይታይ፡፡ የተባለው ነገር በማስረጃ ቀርቦ እንጂ በግምት ሊሆን አይገባም፡፡ ፍርድ ቤቱ ‹በዝግ ችሎት ሂደቱ ይታይ› ብሎ የሚወስን ከሆነ ዛሬውኑ የምትፈርዱብንን ተቀብለን ለመመለስ ዝግጁ ነን፡፡ አቃቤ ህግም ሆነ እናንተ የግፍ እስረኞች መሆናችንን ታውቃላችሁ ብለን እናስባለን፡፡›› ሲል ተናግሯል፡፡

ሶስቱም ዳኞች ‹‹የአቃቤ ህግን አቤቱታና በተከሳሾች በኩል የቀረበውን አስተያየት በጽ/ቤት ተመካክረን ተመልሰን እንወስናል›› ብለው ከችሎት ወጥተው ከ30 ደቂቃ በኋላ በመመለስ ጉዳዩን መመርመራቸውን የቀኝ ዳኛው ገልጸው፤ ችሎት በዝግ የሚታይበትን ሁኔታ በህገ-መንግሥቱና በሌሎች ህጎች ላይ የተደነገጉትን ፍሬ ነገሮች በመዘርዘር ‹‹የአቃቤ ህግን አቤቱታ በማስረጃ ያልተደገፈ በመሆኑ አልተቀበልነውም፤ የምስክሮች ስምና ቃል ግን በህተመት እና በኤሌክትሮኒኪስ ሚዲያ እንዳይዘገብ ወስነናል›› የሚል መልስ ከሰጡ በኋላ ምስክሮችን ወደማድመጥ ሂደት ገብተዋል፡፡ የቃቤ ህግን ምስክሮች የማድመጥ ሂደት እስከፊታችን ሐሙስ ሰኔ 04 ቀን 2007 ዓ.ም ዕለት ድረስ እንደሚዘልቅ ዳኞች ተናግረዋል፡፡

 

Previous Story

ምርጫ ሲባል መሳይና አስመሳይ – መስፍን ወልደ ማርያም

Next Story

ገዳይና ሟች – አየር ኃይልና ህውሃት (ከ አዲስ)

Zehabesha | Ethiopian Latest News, Top Analysis & Best Articles <h1 style="text-align:center">tHE HABESHA Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win</h1><title> <title><h2 style="text-align:left">Get the Best Scholarly Articles and Analysis on ZeHabesha</h2><title> <title><h3 style="text-align:right">Zehabesha Ethiopian News</h3><title> <title><h4 style="text-align:justify">Ethiopian Lates News</h4><title> <meta name="keywords" content="Ethiopian News, Ethiopia News, Ethiopian News Today, Top Stories, The Habesha, Latest News, Ethiopia, Breaking News, zehabesha, zehabesha Amharic News, The Habesha News, Headlines, borkena. bbc amharic, repoter, mereja, Ethiopian News provider"> <!-- Google Tag Manager --> <script>(function(w,d,s,l,i){w[l]=w[l]||[];w[l].push({'gtm.start': new Date().getTime(),event:'gtm.js'});var f=d.getElementsByTagName(s)[0], j=d.createElement(s),dl=l!='dataLayer'?'&l='+l:'';j.async=true;j.src= 'https://www.googletagmanager.com/gtm.js?id='+i+dl;f.parentNode.insertBefore(j,f); })(window,document,'script','dataLayer','GTM-5WDL6STX');</script> <!-- End Google Tag Manager --> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=G-W9E3TWE2TL"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'G-W9E3TWE2TL'); </script> <meta name="msvalidate.01" content="4781C31A916C7AB883D8AF1F4F3BFC49" /> <link rel="icon" href="/path/to/favicon.ico"> <link rel="icon" type="image/png" href="/thehabesha.com/favicon-96x96.png" sizes="96x96" /> <link rel="icon" type="image/svg+xml" href="/thehabesha.com/favicon.svg" /> <link rel="shortcut icon" href="/thehabesha.com/favicon.ico" /> <link rel="apple-touch-icon" sizes="180x180" href="/thehabesha.com/apple-touch-icon.png" /> <link rel="manifest" href="/thehabesha.com/site.webmanifest" /> <meta name="seobility" content="48b995a16caf3ab9d546a000c18b65d3"> <main> <!-- Main content of your page goes here --> </main> <script type="text/javascript" src="//cdn.rlets.com/capture_configs/d2b/aac/e54/1fc4f7ea32cf1e1d818a0f2.js" async="async"></script> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=TAG_ID"></script> <script src="https://www.googleoptimize.com/optimize.js?id=OPT-M8Z33GL"></script> <meta name="google-site-verification" content="Lf_65x5pXGn-W1TA8CsfJi-53aAyIKdfVyM_QkwpvgY" /> <head> <title>Ethiopian Latest News: Top Analysis and the best Articles<title> <script defer data-domain="thehabesha.com/mEUHSv" src="https://api.publytics.net/js/script.manual.min.js"></script> <script> window.publytics = window.publytics || function() { (window.publytics.q = window.publytics.q || []).push(arguments) }; publytics('pageview'); </script> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=UA-215686007-9"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'UA-215686007-9'); </script> <script async src="https://pagead2.googlesyndication.com/pagead/js/adsbygoogle.js?client=ca-pub-9091845805741569" crossorigin="anonymous"></script> <script async custom-element="amp-ad" src="https://cdn.ampproject.org/v0/amp-ad-0.1.js"></script> <title>Zehabesha Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win