በጋሞ ጎፋ ዞን ኮንሶ ወረዳ በምርጫ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ ስምንት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን የዞኑ የፓርቲው አስተባባሪ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
አባላቱ ከመጋቢት 9/2007 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ በእስር ላይ የሚገኙት ስምንቱ ሰዎች የሚከተሉት ናቸው፡-
1. ካርታ ካርኪ
2. ኩንሳ ካፒሊ
3. ታሪኩ አንካሶ
4. ካያና ካላታ
5. ገላዬ ካይድራ
6. ካርታ ሀይቶ
7. ኩንሱ ካምባ
8. ሆዳ ሆልጥሽ