በኢትዮጵያ የሚገኘው የናይጄሪያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ ዜጎቹ ማስጠንቀቅያ ሰጠ

January 12, 2019

በአፍሪካ ህብረትና በአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ቋሚ መልእክተኛና የናይጄሪያ አምባሳደር ቃል አቀባዩ ካስተን ኦጆሞ ዛሬ በአቡጃ በሰጡት መግለጫ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ናይጄሪያዊያን ከ3 ሺህ ዶላር በላይ

https://www.youtube.com/watch?v=G6LalCqO72M
የሚበልጥ ገንዘብና ውድ ጌጣጌጦችን እንዳይዙ አሳስበዋል፡፡ ይህን ማሳሰቢያ የሰጡትም በኢትዮጵያ ህግ አስከባሪዎች ንብረታቸው እንዳይወረስባቸው በማሰብ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በመግለጫቸው ‹‹ከ3 ሺህ ዶላር የሚበልጥ የውጭ ምንዛሬ ወይንም የዚህ ተመጣጣኝ የሆነ ገንዘብ የምትይዙ ከሆነ ልክ ኢትዮጵያ እንደገባችሁ ለገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ማስታወቅ አለባችሁ፡፡›› ማለታቸውን ዛሬ የናይጄሪያ ጋዜጦች ዘግበውት ተመልክተናል፡፡

Previous Story

30 በሬዎች በህገ ወጥ መንገድ ከኢትዮጵያ ሊወጡ ሲሉ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ

Next Story

ለቀናት ታግተው የተለቀቁት የደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት ‹‹እኔ ፖለቲካ አይመለከተኝም፣ ያገቱኝ ሰዎችም የተሳሳቱ ይመስለኛል›› አሉ

Go toTop